ጅማ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ዘመናዊ የህክምና ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ሌሎችች ባለስልጣናት በተገኙበት ይመረቃል

Home Forums Semonegna Stories ጅማ ዩኒቨርሲቲ ያስገነባው ዘመናዊ የህክምና ማዕከል ጠቅላይ ሚኒስትሩ እና ሌሎችች ባለስልጣናት በተገኙበት ይመረቃል

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • Author
    Posts
  • #8853
    Semonegna
    Keymaster

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ ባስገነባው የህክምና ማዕከል ምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን ያስመርቃል።

    ጅማ (ሰሞነኛ)– ጅማ ዩኒቨርሲቲ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) እና ሌሎች ከፍተኛ የፌድራልና የክልል መንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት የህክምና ማዕከሉን ኅዳር 29 ቀን 2011 ዓም እንደሚያስመርቅ ተዘግቧል።

    የህክምና ማዕከሉ 800 (ስምንት መቶ) አልጋዎች ያሉት ሲሆን፥ በደቡብ ምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል ከ20 ሚሊየን በላይ ሰዎች የህክምና አገልግፍሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው ተብሏል። ማዕከሉ እንደ ደቡብ ሱዳን ላሉ ጎረቤት ሀገራትም አገልግሎት ለመስጠት ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ መሆኑን ተነግሯል።

    ዩንቨርሲቲው ያስገነባው ይህ የህክምና ማዕከል በህክምና እና ጤናው ዘርፍ የምርምር፣ የማስተማሪያ፣ እንዲሁም የማኅበረሰብ አገልግሎቶችን ለመስጠት የሚያስችል መሆኑም ነው የተገለጸው። በዚህም ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሀገሪቱ ከሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ሲነጻጸር ልቆ የሚታይበትን የማኅበረሰብ ተኮር (community-based) ትምህርትና ምርምር ይበልጥ ያገለብትለታል ተብሎ ይታመናል።

    Ethio-American Doctors Group (EADG): Building a regional healthcare system & medical tourism

    ዩንቨርሲቲው በህክምና ማዕከሉ የምረቃ ሥነ ስርዓት ላይ ለዓመታት ያስተማራቸውን 331 የህክምና ዕጩ ምሩቃን እና በተለያዩ መስኮች ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ 2ሺህ የድህረ ምረቃ መርሀ ግብር ተማሪዎችን እንደሚያስመርቅም ታውቋል።

    በተመሳሳይ መልኩ ዩንቨርሲቲው ያስገነባው 40 ሺህ ያህል ተመልካቾችን ማስተናገድ የሚችለው ስታዲየም፣ ሲቭክ አዳራሽ፣ መንገዶችና ሌሎች የመሠረተ ልማት ሥራዎች ይመረቃሉ ተብሏል። የሲቪክ አደራሹ በርካታ ተሰብሳቢዎችን በአንዴ የሚያስተናግድና የተለያዩ ኮንፈረንሶችን በተመሳሳይ ጊዜ ለማካሄድ የሚያስችሉ የተለያዩ ክፍሎች እንዳሉትም ተነግሯል። ከዚህ ጋር ተያይዞ እንደተዘገበው ይህ የሲቭክ አዳራሽ ከተማዋን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ታሳቢ ተደርጎ የተገነባ ስለመሆኑም ነው የተገለጸው።

    ምንጭ፦ ኢቢሲ / ኤፍ.ቢ.ሲ. / ሰሞነኛ ኢትዮጵያ
    ——
    ተመሳሳይ ዜናዎች፦

    ጅማ ዩኒቨርሲቲ የህክምና ማዕከል


    #8870
    Anonymous
    Inactive

    የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል ተመረቀ

    ኢትዮጵያ፣ የሱዳንና የጂቡቲ መሪዎች የጅማ ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታልን መረቁ።

    ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ከሱዳኑ ፕሬዝዳንት ኦማር ሀሰን አልበሽር እና ከጅቡቲው ፕሬዝዳንት እስማኤል ኦማር ጌሌ ጋር በመሆን ነው ሆስፒታሉን ዛሬ የመረቁት።

    ሆስፒታሉ 800 የመኝታ ክፍሎች ያሉት ሲሆን በደቡብ ምዕራብ የአገሪቱ ክፍል ለሚገኙ ከ20 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የህክምና አገልግሎት መስጠት የሚችል ነው።

    እንዲሁም ለደቡብ ሱዳን እና አጎራባች አገሮች የህክምና አገልግሎት እንዲሰጥ ተደርጎ የተገነባ ነው።

    ሆስፒታሉ ከጤና አገልግሎቱ ባሻገር የምርምር፣ የማስተማሪያና የማህበረሰብ አገልግሎቶችን ለመስጠት ያስችላል።

    መሪዎቹ የህክምና ትምህርታቸውን ተከታትለው ያጠናቀቁ 300 ተማሪዎችንም ይመርቃሉ ተብሎ ይጠበቃል።

Viewing 2 posts - 1 through 2 (of 2 total)
  • You must be logged in to reply to this topic.